ይህ የአማራ ትሥሥርር በቻይና ይፋዊ ድረ-ገጽ ነው። በዚህ ድረ-ገጽ የአማራን ሕዝብ ታሪክ፣ ሃይማኖት፣ ባሕል፣ ልማድ፣ አርበኝነት፣ ቅርስ እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮችንም ጭምር ለአባላት በሚገባ እናሳውቃለን። የድረ-ገጹ ዋና አላማ የአማራን ታሪክ በሚገባ ለሁሉም በማስተማር ታሪካችንን ወደቀደመ ልዕልናው መመለስ ነው። አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፤ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ፤ አንዲት ነጻ ሃገር ኢትዮጵያ -->

Happy Birth day for Emperor Menelik II and Empress Tayitu Bitul

እንኳን ለንጉሡ እምዬ ምኒልክ(ዳግማዊ ዓጤ ምኒልክ፻፸፰ ዓመት እና ንግሥቲቱ እቴጌ ጣይቱ ብጡል(ብርሐን ዘኢትዮጵያ፻፹፪ ዓመት የልደት በዓል አደረሳችሁ።

💫ዳግማዊ ዓጤ ምኒልክአባታቸው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴ እና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም ቅዳሜ ነሐሴ 12 ቀን 1836 ዓ.ም ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወለዱ።💫

ድሃ ከወደደበት ቦታ ይቀመጥ፤ በዘር በወገን ልዮነት አይከልከል።  ዳግማዊ አጤ ሚኒሊክ

ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ግዜ ሃበሻ።


 ጥቁሩ የነጭ ጌታ ዳግማዊ አጤ ምኒልክ

                           እቴጌ ጣይቱ

💫እቴጌ ጣይቱ ብጡል ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ነሐሴ 12 ቀን 1832 ዓ.ም  በጎንደር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ በሚል ቅፅል ስም ይታወቃሉ።💫

ትውልድ ተጨንቆ አፈና ይዞት፣

ዓለም ተደሰተ ፀሐይ ወጣለት። 

እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አሎድም ኢትዮጵያን የጣሊያን የሚያደርጋት ውል ከመፈረም ግን ጦርነት እመርጣለው።


ዳግማዊ አጤ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል

ታላቁን ጥቁር ሰው እምዬ ምኒልክን ለመዘከር በዓለም በሚገኙ ሀገራት የተሰየሙ መታሰቢያዎች 

፩. በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ በምኒልክ ስም የተሰየመ መንገድ፣

፪. በለንደን ከተማ በምኒልክ የተሰየመ መንገድ፣

፫. በጅቡቲ በምኒልክ የተሰየመ ሆቴል፣

፬. በደቡብ አፍሪካ በምኒልክ የተሰየመ ሽቶ፣

፭. በቤልጂየም በምኒልክ የተሰየመ ቢራ፣

፮. በብራዚል በምኒልክ የተሰየመ ካፌ፣

፯. በብራዚል በምኒልክ የተሰየመ ጋዜጣ፣

፰. በፈረንሳይ በምኒልክ የተሰየመ ቸኮሌት ...ወዘተ ይገኛሉ።

[ሙሉ ታሪኩን በዚሁ ገጽ ላይ እናቀርባለን...]

የአማራ ትስስር በቻይና(ANiC)

የአማራ ሕዝብ የሚያኮራ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ስነጽሑፍ፣ ሃይማኖትና ባህል ያለው፤ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ባለቤት የሆነ፤ ሃገር የሰራ፣ ነጻነቱን ያስጠበቀ፤ የራሱ የሆነ ፊደል ያለው፤ የጥንታዊ ትምህርት ስርዓት ባለቤት የሆነ ጀግናና ኩሩ ሕዝብ ነው። የአማራ ሕዝብ በሃገረ መንግስት ምስረታ ሃገርን ከወራሪ መጠበቅና ዳር ድንበሯን በማስጠበቅ ታላቅ ገድል በመስራት እኛ ልጆቹ ቀና ብለን እንድንሄድ አድርጎናል።

1 Comments

  1. እንኳን አብሮ አደረሰን! ታሪኩ ግን ይለቅልነ

    ReplyDelete
ቀዳሚ ገጽ ተከታይ ገጽ
hi